22 Jun 2026, Mon

ኢዜማ 1 ወንበር ባሸነፈበት የኦሮሚያ ምክር ቤት መቀመጫ ያላገኘው ኦነግ በአዲስ አበባ 2 ወንበር አሸነፈ ፤

በሰባተኛው የኢትዮጵያ አጠቃላይ ምርጫ በኦሮሚያ ምክር ቤት አንድም ወንበር ያላሸነፈው ኦነግ፤ በአዲስ አበባ ምክር ቤት ሁለት ወንበር ሲያገኝ ኢዜማ ደግሞ በኦሮሚያ ምክር ቤት አንድ መቀመጫ አገኘ።

ብልጽግና አብዛኛውን መቀመጫ ባሸነፈበት አጠቃላይ ምርጫ 40 የተቃዋሚ ፓርቲ ዕጩዎች እና ስምንት የግል ተወዳዳሪዎች ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት መቀመጫ አሸንፈዋል።

ውድድር ከተደረገባቸው 501 የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት መቀመጫዎች ገዢው ብልጽግና ፓርቲ ለተጨማሪ አምስት ዓመታት በሥልጣን ላይ ለመቆየት የሚያስችለውን 438 አሸንፏል።

በምርጫው ከተሳተፉ ተቃዋሚ የፖለቲካ ፓርቲዎች መካከል ከፍተኛውን የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት መቀመጫ ያገኘው የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትሕ (ኢዜማ) ሲሆን 13 መቀመጫዎችን አሸንፏል።

ስምንት የግል ዕጩዎች፣ የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (አብን) 6፣ የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዴሞክራሲያዊ አንድነት መድረክ (መድረክ) 3፣ የአማራ ዴሞክራሲያዊ ኃይል ንቅናቄ 3፣ ነጻነት እና እኩልነት ፓርቲ 3፣ ትብብር ለኢትዮጵያ አንድነት ፓርቲ 2 መቀመጫዎችን ሲያሸንፉ አምስት ፓርቲዎች ደግሞ አንድ አንድ መቀመጫ አግኝተዋል።

በተጨማሪም ብልጽግና ምርጫ በተካሄደባቸው 11 የአገሪቱ ክልሎች ውስጥ እንዲሁም በዋና ከተማዋ አዲስ አበባ እና በድሬ ዳዋ ምክር ቤቶች ውስጥ ካሉት መቀመጫዎች አብዛኛውን አግኝቷል።

ብልጽግና በፌደራል፣ በክልል እና በከተሞች መንግሥት ለመመሥረት የሚያስችለውን የምክር ቤት መቀመጫዎችን አሸንፏል።

በዚህም የኦሮሚያን 523፣ የአማራ 257፣ የሶማሌ 214፣ የሲዳማ 175፣ የጋምቤላ 176፣ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ 143፣ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ 144፣ የደቡብ ኢትዮጵያ 182፣ የቤኒሻንጉል ጉሙዝ 145፣ የአፋር 124፣ የሐረሪ 32፣ የአዲስ አበባ 134 እና የድሬዳዋ 161 የምክር ቤት መቀመጫዎችን ዕጩዎቹ አሸንፈዋል።

በቴሌግራም ይቀላቀሉ
👇🏽👇🏽👇🏽👇🏽👇🏽
https://t.me/utopiatowday


Discover more from ኢትዮጵያ ዛሬ ፤

Subscribe to get the latest posts sent to your email.

Leave a Reply

Discover more from ኢትዮጵያ ዛሬ ፤

Subscribe now to keep reading and get access to the full archive.

Continue reading